image
image
image
image
image

የክፍለ ከተማው አስተዳደር ካቢኔ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውይይት አደረገ።

መስከረም 18, 2017
የልደታ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የካቢኔ ውሳኔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት በማድረግ የውሳኔ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። በውይይቱም በክፍለ ከተማው አስተዳደር ጽ/ቤቶች የቀረቡ ጥያቄዎችን እና አፋጣኝ ምላሽ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት በማካሔድ የነዋሪዎች የልማትና የመልካም አስተዳደር ችግሮች ሊፈቱ የሚችሉ ውሳኔዎች ማሳለፍ ተችሏል። የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ ለአስተዳደሩ ካቢኔ አባላት የቀረቡ አጀንዳዎች የነዋሪዎችን ተጠቃሚነትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን የሚፈቱ በመሆናቸውና የአስተዳደሩን ቀጣይ ስራዎች የሚያቀላጥፉ በመሆናቸው የተቀመጠው የውሳኔ ሀሳብ ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት አመላክተዋል። የካቢኔ አባላቱ ከውሳኔ ባለፈ አስተዳደሩ የጀመራቸውን የኢኒሼቲቭ ስራዎች ያሉበት ደረጃ የገመገመ ሲሆን እስካሁን የተሰሩ ተግባራት አበረታች መሆናቸው ታይቷል። በተለይ ሰው ተኮር ስራዎቹ ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው እና 7/24 በሚለው መርህ መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ ተቀምጧል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች