image
image
image
image
image

በከ/ከተማው ስር የሚገኙ 10ሩወረዳዎች እና የክ/ከተማ ፅ/ቤቶች ለመመዘን የሚያስችል የምዘና አተገባበር ላይ በየደረጃው ለሚገኙ ኃላፊዎች ኦረንቴሽን ተሰጠ

መጋቢት 17, 2017
በክ/ከተማ አስተዳደሩ ስር የሚገኙ የክ/ከተማ ፅ/ቤቶች እና ወረዳዎች የአፈፃፀም ምዘና ለማከናወን እንዲቻል ምዘና አተገባበር ሰነድ ላይ ለወረዳ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ፅ/ቤት ኃላፊዎች፣ ለወረዳ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፅ/ቤት ሀላፊዎች:ለፕላን እና መልካም አስተዳደር ስራ ሂደቶች አሬንቴሽን ተሰጥቷል የምዘና ትግበራ ሂደት አተገባበር ሰነድ ያቀረበ ሲሆን ምዘናው በጥምረት የሚካሄደው ሆኖ ምዘና በዋናነት በምዘና ሂደት የሚታዩ ክፍተቶችንና ቅሬታዎችን በመቀነስ ከክ/ከተማ እስከ ወረዳ ያለውን የምዘና አፈፃፀም ወጥነት እና ተመሳሳይነት ባለው መስፈርት በተቀናጀ መልኩ ለመመዘን እዲቻል ታሳቢ ተደርጎ መዘጋጀቱን ተገልፇል::የምዘና ትግበራ ሂደት፣ የመዛኝ ኮሚቴ አባላት አደረጃጀት፣ በምዘና ሂደትና ውጤት ላይ የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ስርዓት፣ የድረ ምዘና ስራዎች እና የአስፈፃሚ አካላት ሚና ጨምሮ መሰል ተግባራትን በዝርዝር ውይይት። በቀረበው ሰነድ ላይ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብ እና አስተያየት ተሰቶባቸዋል። ከዚህም ጋር የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማማት ፅ/ቤት ሀላፊ ባስተላለፉት መልዕክት ከዚህ ቀደም ሶስቱ ተቋማት የተለያየ እና ድግግሞሽ ያለው የምዘና ሂደት ያከናውኑ እንደነበር አስታውሰው ተቋማትን ወደ ተቀራረበ አፈፃፀም እንዲመጡ ለማድረግ ወጥነት ያለው የምዘና ስርዓት መዘርጋቱን ገልፀዋል። የፕላንና ልማት ሀላፊ አቶ ክብረት የምዘና ሂደቱ የተቀመጠውን መስፈርት ተከትሎ የሚከናወን በመሆኑ ስራዎችን በብቃት የሚፈፅሙትን ተቋማት ለማበረታታት እና ክፍተት የሚታይባቸውን ተቋማት ከከፍተታቸው እንዲወጡ ለማስቻለ መሆኑን ገልፀው በእውቀት ላይ የተመሰረተ ለአንድ አላማ የሚከናወን ምዘና በመሆኑ ተቋማት የተሰጣቸውን ኃላፊነት በትኩረት እንዲያከናውኑ አሳስበዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች