image
image
image
image
image

በልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር በወረዳዎች አስተዳደር የሚሰጡ አገልግሎቶችን አስመልክቶ ድንገተኛ ምልከታ ተደረገ።

ህዳር 24, 2017
የአገልግሎት ቀንን ምክንያት በማድረግ የልደታ ክፍለ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ፣የመልካም አስተዳደርና ቅሬታና አቤቱታ ፅህፈት ከኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን የአገልግሎት ቀንን በማስመልከት በልደታ ወረዳ 5,3 ና 10 አስተዳደር አገልግሎት አሰጣጡን ምልከታ አደረጉ፡፡ የአገልግሎት አሰጣጡ ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሎች እየታዩበት መሆኑ በምልከታው የተገለጸ ሲሆን ፡ ምልከታውን አስመልክቶ በክ/ከተማው በወረዳ 05,03 ና 10 አስተዳደር ስር የሚገኙ የስራና ክህሎት፣ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት፣ሲቪል ምዝገባና የህዝብ አገልግሎት ፥ቤቶች ጽ/ቤቶችን እና የአንድ ማዕከል አገለግሎትን እንዲሁም የስራ ቦታ ምቹነትን መሰረት ያደረገ ምልከታ ተደርጋል፡፡ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሎች እየታዩበት መሆኑ፥ በተለይም የአንድ ማዕከል አገለግሎት በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ መሆኑንና እና የህጻናት ማቆያ ስፍራዎችም በተሻለ ሁኔታ አገልግሎት እየሰጡ መሆናቸውን በማውሳት ከሰራተኞች ደረት ባጅ አጠቃቀምና ስታንዳርድ ምዝገባ እንድውም የኔት ወርክ መቆራረጥ ጋር በተያያዘ ውስንነቶች መኖራቸውን የልደታ ኮሚንኬሽን ፅ/ቤት ከህዝብ አስተያየት ባአገኘው መረጃ አመልክቷል። ፈጣን ቀልጣፋና ከእጅ መንሻ የፀዳ አገልግሎት ለሁሉም ማህበረሰባችን !!!!!

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች