image
image
image
image
image

የ2017 በጀት አመት በግማሽ አመት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ዝግጅትና ምዘና እንዲሁም የመካከለኛ ዘመን (2013-2017) የአራት አመት እቅድ አፈፃፀም ውይይት ተደረገበት።

ታህሳስ 21, 2017
በውይይቱም የ4 ዓመት የጽ/ቤቶች አፈፃፀምና የሪፖርት ቢጋር ለወረዳ አመራሮችና ለክፍለ ከተማ ቡድን መሪዎች በማቅረብ ውይይት ተደርጓል የልደታ ክፍለ ከተማ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ጢቂ ድሪባ እንደገለፁት ወጥ የሆነ ቢጋር በማዘጋጀትና የተቋማትን አፈፃፀሙን በጋራ በመመዘን ቀልጣፋ የሆነ አሰራር እንዲፈጠር ይረዳል በማለት በእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት አዘገጃጀት የነበሩ ክፍተቶች በማረም በጥንካሬ የሚጠቀሱ ጉዳዮች በማስቀጠልና ሁሉም የተሻለ ግንዛቤ ኖሮት በትኩረት መሠራት አለበት በማለት ገልፀዋል። አቶ ጢቂ አያይዘው በወቅቱ ሪፖርት በማዘጋጀት በመገምገም ለሚመለከተው አካል በጊዜው በመላክ ጊዜውን የጠበቀ ሪፖርት እንድንሰራ የናንተ ሚና ከፍተኛ ነው በማለት ተቋሞች በቢጋሩ መሰረት ሪፖርት ማዘጋጀት በቀኑ መላክ ይኖርባቸዋል ሲሉ ገልፀዋል። የልደታ ክፍለ ከተማ ፕላንና ልማት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ክብረት እንደተናገሩት የተቋማት እቅዶችን በመካከለኛና በረዥም ጊዜ አድርጎ በመከፋፈል አፈፃፀማቸውን በመወያየት እንዲከለሱ በማድረግና የ5 አመት አፈፃፀም በታቀደው መሠረት እንዲፈፀም ይረዳል በማለት ሁሉም ተቋማት አፈፃፀሙን በማየትና መገምገም ቀሪ ተግባራትን አካቶ መስራት ይገባል በማለት ገልፀዋል አቶ ክብረት አክለው የጽ/ቤቶች ሪፖርት በቢጋሩ መሠረትና ጊዜውን የሚመጥንና የተቀላጠፈ እንዲሆን ተቋማት ሚናቸው ጉልህ በመሆኑ አንስተው ሶስቱ ሴክተሮችም ሪፖሪቶችን በማየትና ወጥ የሆነ ምዘና ማካሄድ ይችላሉ በማለት ገልፀዋል። ተሳታፊዎችም በተናጠል ስንሄድ ሲደረግ የነበረው የምዘና ስርዓት አሁን በጋራ ሆኖ መሠራቱ የተሻለ እና ወጥ የሆነ መሆኑ ቀልጣፋና ውጤታማ ያደርገዋል በማለት አንስተዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች