image
image
image
image
image

የልደታ ክ/ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ፅ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን ገመገመ።

ሚያዚያ 28, 2017
በግምገማው ከወረዳ የተውጣጡ የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ፅ/ቤት ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች እንዲሁም ባለደርሻ አካላት የተሳተፉ ሲሆን የተገልጋይና የሰራተኛ እርካታ ከማሳደግ ፣ ብቁ የሰው ሀይል ከመገንባት፣ የስልጠና ጥራትና ተደራሽነት፣ አደረጃጀትና አሰራር ማሻሻል፣ በስታንዳርድ መሰርት የሚሰጡ አገልግሎቶች ፣ የስታንዳርዳይዜሽን እና ምቹ የስራ ሁኔታን ከመፍጠር አንፃር የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦዋል። የጽ/ቤቱ ሀላፊ አቶ ጢቂ ድሪባ ህዝብና መንግስትን ከሚያስተሳስሩ ጉዳዮች መካከል አንዱና ዋነኛው የአገልግሎት አሰጣጥ በመሆኑ የህዝብን እርካታ ለማረጋገጥ ተቋማት በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ መሰረት መስራት ይገባቸዋል ብለዋል። በመድረኩ ለተነሱ ሀሳብና አስተያየቶች ምላሽ የሰጡት በፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ፅ/ቤት የአስተዳደር እና ፋይናንስ ፅ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ኢየሩሳሌም እንደተናገሩት ጠንካራ ተቋም የሚለየው በሚሰጠው የአገልግሎት ጥራት ላይ ተመስርቶ በመሆኑ አመራሩ ተግባራት በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ እንዲሰጡ የማድረግ ሀላፊነቱ የጎላ ነው ያሉ ሲሆን ስራዎችን እየገመገሙ መሄድ ወጥነት ያለው የአሰራር ስርአት ለመዘርጋት እንደሚያስችል ገልፀዋል። ወረዳ 6፣9 እና 10 አፈፃፀማቸውን ያቀረቡ ሲሆን ሰፊ ውይይትም ተደርጎበታል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች